Phone:

666 888 0000

ኢሜይል:

contact@h4peace.org

ጽሑፎች

የአገዛዙ ህዝብን ከህዝብ የማዋጋት ዳግም ሴራ ሊከሽፍ ይገባል!

የአገዛዙ ህዝብን ከህዝብ የማዋጋት ዳግም ሴራ ሊከሽፍ ይገባል! ከተስፋ ለሰላም የተሰጠ መግለጫ   መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም. ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን መምጣት በኋላ በኢትዯጵያ ውስጥ በሺ የሚቆጠሩ ግጭቶች ተከስተዋል። በሰሜኑ የአገራችን ክፍልና በኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ህዝብ ጨራሽ ጦርነቶች ተካሂደዋል፣ አሁንም በመካሄድ ላይ ይገኛሉ። ከአንድ አመት በፊት በፕሪቶርያው ስምምነት የቆመው የአማራና የአፋር ክልሎችን ጨምሮ በዋናነት በትግራይ በተካሄደው ጦርነት ብቻ በታሪካችን አይተነው በማናውቅ መጠን ከ1 ሚሊየን በላይ የሆነ ህዝብ እንደሞተና ከ4 ሚሊየን የበለጠ ህዝብ ከመኖሪያ ቀየው እንደተፈናቀለ ይገመታል። እነዚህ

ሙሉውን ጽሑፍ ያንብቡ »

ጦርነትና ውድመት ይቁም! – የሰላም ለተስፋ ስብስብ ጥሪ

ታህሳስ 29 ቀን 2016 ዓ.ም ጦርነትና ውድመት ይቁም! የሰላም ለተስፋ ስብስብ ጥሪ ኢትዮጵያ ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በታሪኳ አይታው በማታውቀው እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በማለፍ ላይ ነች። ከመቶ ሃያ ሚሊዮን በላይ በሆነው ህዝቧ የአፍሪካን ህዝብ 10 በመቶ ድርሻ ያላት ይህች ጥንታዊት አገር ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ በሚታትሩ የውስጥና የውጭ ሀይሎች በቀውስና በብጥብጥ እየተመሰቃቀለች ትገኛለች። በህዳር 2015 ዓ.ም. የተፈረመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በሚያስችል አግባብ ባለመፈጸሙ ምክንያት ፈንጥቆ የነበረው ተስፋ ልብ በሚሰብር ሁኔታ የመደናቀፍ አደጋ ገጥሞታል። ስምምነቱ ከተፈረመ ከአመት በዃላም እንኳ በሰሜኑ

ሙሉውን ጽሑፍ ያንብቡ »

የተስፋ ለሰላም ስብስብ መቋቋምን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ

  መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም የተስፋ ለሰላም ስብስብ መቋቋምን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ “ተስፋ ለሰላም” ለዘመናት የኖረ ትስስርና ዝምድና ባላቸው የአማራና የትግራይ ማህበረሰቦች መካከል ያለው የእርስ በርስ ቅራኔና ግጭት አብዝቶ ባሳሰበንና ከሁለቱም ወንድማማችና እህትማማች ማህበረሰቦች ተወላጅ በሆንን ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ የሰላም አጀንዳ አራማጅ ስብስብ ነው። ዓላማችንም በአማራና በትግራይ ማህበረሰቦች መካከል ባለፉት አመታት እየተባባሰ የመጣውና በተለይም በቅርቡ በተካሄደው ጦርነት ምክንያት የተፈጠረው ቅራኔ እንዲወገድና ወደተሻለ ሰላማዊ ግንኙነት እንዲቀየር ጥረት ማድረግ ነው። ለ “ተስፋ ለሰላም” መፈጠር መነሻ የሆነው ዋናው ምክንያት በእነዚህ በሃይማኖት፣

ሙሉውን ጽሑፍ ያንብቡ »
ይፈልጉ
በማህበራዊ ሚዲያ ያጋሩ